ጥር 12፣ 2017 - ‘’የራያ አላማጣ ዞን በመንግስት በኩል ተዘንግቷል’’
- Jan 20, 2025
- 1 min read
‘’የራያ አላማጣ ዞን በመንግስት በኩል ተዘንግቷል’’ ሲሉ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰየሙት አስተዳዳሪ ተናገሩ፡፡
አካባቢው በ #ኮማንድ_ፖስት እየተዳደረ ቀጥሏል ተብሏል፡፡
በራያ አላማጣ፣ ኮረም፣ ወፍላ፣ ዛታና የተለያዩ ወረዳዎች ዛሬም የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዝግ እንደሆኑ ነው፡፡

የትምህርት የጤናና ሌሎች መሰረታዊ የሚባሉ ነገሮች በአብዛኛው እየተሰጡ እንዳልሆነ ሰምተናል።
የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያቆሙት ከ #ፕሪቶሪያው_የሰላም ስምምነት በኋላ መሆኑን ዞኑ ለሸገር ሬዲዮ ተናግሯል፡፡
ከዚህ ቀደም #በመንግስት_ስራ ላይ የነበሩ ሰራተኞች እጃቸውን አጣጥፈው ከተቀመጡ ሰንበትበት ማለታቸውንም ነግረውናል፡፡
ከአንድ ዓመት በላይ ዝግ የሆኑት እነዚያ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ ስራ የሚገቡት መቼ ነው የሚለው የማህበረሰቡ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል፡፡
ዞኑ ከፌዴራል ወይም ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲሁም ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ቀደም ብሎ ስፍራውን ሲያስተዳደር በነበረው የአማራ ክልል በኩል ቋሚ በጀት አልተያዘለትም ተብሏል፡፡
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5rs
_edited.jpg)


Helpful explanation of inclusive writing with clear examples and practical alternatives. Thank you for making this topic easier to understand. Greetings from Loteria Mundial, wishing you continued success!
Snow Rider is a fast-paced endless runner game that puts you in the driver’s seat of a sled racing down snowy hills.