top of page

ጥር 12፣ 2015- የሴራሊዮን ፓርላማ የሴቶችን መብት ፣ ኑሮ እና የሥራ ሁኔታ የሚያሻሽል ሕግ አፀደቀ

  • sheger1021fm
  • Jan 20, 2023
  • 1 min read

የሴራሊዮን ፓርላማ የሴቶችን መብት ፣ ኑሮ እና የሥራ ሁኔታ የሚያሻሽል ሕግ አፀደቀ፡፡


ሕጉ 30 በመቶዎቹ የስራ ቦታዎች በሴቶች እንዲያዙ የሚጠይቅ መሆኑን ብሉምበርግ ፅፏል፡፡


የስራ ቦታዎች ድልድሉ የግል ድርጅቶችንም እንደሚጨምር ታውቋል፡፡


ሴቶች በስራ ቦታዎች የእኩል መብት እና ስልጠናዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ሕግ መሆኑ ተነግሮለታል፡፡


ከ25 ያላነሱ ሰዎች ቀጥረው በሚያሰሩ ድርጅቶችም ህጉ ተፈፃሚ እንደሚሆን ታውቋል፡፡


የሴራሊዮን መንግስት ህጉ የፀደቀበትን እለት ታሪካዊ ሲል ማሞካሸቱን ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page