top of page

ጥር 12፣ 2015- አሜሪካ እና አጋሮቿ ለዩክሬይን ተጨማሪ የጦር መሳሪያ እርዳታቸውን ሊያጎርፉላት ነው ተባለ


አሜሪካ እና አጋሮቿ ለዩክሬይን ተጨማሪ የጦር መሳሪያ እርዳታቸውን ሊያጎርፉላት ነው ተባለ፡፡


አሜሪካ ብቻ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የዋጋ ግምት ያላቸው ብረት ለበስ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና የአየር መከላከያዎችን ለዩክሬይን ለማቅረብ መሰናዳቷን ዴፌንስ ብሎግ ፅፏል፡፡


ከአሜሪካ በተጨማሪ ብሪታንያ፣ ፖላንድ፣ ላቲቪያ፣ ኔዘርላንድስ፣ ስሎቫኪያ ለዩክሬይን የጦር መሳሪያዎችን እንልካለን ካሉ አገሮች ከብዙ በጥቂቱ ናቸው ተብሏል፡፡


አገሮቹ ለዩክሬይን ተጨማሪ የጦር መሳሪያ እና የወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ ቃል ቢገቡላትም ኪየቭ ያስፈልጉኛል ያለቻቸው ከባባድ ዘመን አፈራሽ ታንኮች ግን ከጦር እርዳታው ዝርዝር ውስጥ እንደሌሉ ታውቋል፡፡


ፖላንድ እና ፊላንድ ለዩክሬይን ጀርመን ስርቶቹን ሊዮፓርድ ታንኮችን እንሰጣለን ቢሉም የበርሊን ይሁንታ እንደሚያሻቸው ተጠቅሷል፡፡


አሜሪካ እና አጋሮቿ ለዩክሬይን በሚቀርበው የጦር መሳሪያ እርዳታ ጉዳይ ዛሬ በጀርመን ተሰብስበው እንደሚመክሩ ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page