top of page

ግንቦት 7 2017 - በብቸኝነት በትግራይ ውስጥ ለአንድ ትውልድ ላላነሰ ጊዜ በበላይነት የቆየው ሕወሓት በህጉ መሰረት ተሰርዘዋል መባሉ በክልሉ ምን ሊያጣ ይችል ይሆን?

  • sheger1021fm
  • May 15
  • 1 min read

የትግራይ ህዝብንና የክልሉ ፖለቲካ ብቸኛ ተጠሪ እና ወኪል ነኝ ሲል የነበረውና ከ40 ዓመታት ላላነሰ ጊዜ ክልሉን ሲያስተዳድር የነበረው ሕወሓት ትናንትና ህጋዊ ሰውነቱን ማጣቱ ተነግሯል፡፡


የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ሕ.ወሃት) ከፓርቲነት መዝገብ የተሰረዘው በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሲሆን ህጋዊነቱን የሚያረጋግጡ ስራዎችን ሰርቶ ለቦርዱ እንዲያቀርብ ሕወሓት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ፈቃደኛ ባለመሆኑ በልዩ ሁኔታ የተመዘገበበት ህጋዊነቱ እንዳበቃ ቦርዱ ተናግሯል፡፡


በብቸኝነት በትግራይ ውስጥ ለአንድ ትውልድ ላላነሰ ጊዜ በበላይነት የቆየው ሕወሓት በህጉ መሰረት ተሰርዘዋል መባሉ በክልሉ ምን ሊያጣ ይችል ይሆን? ስንል በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎችን አስተያየት ጠይቀናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….




የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page