top of page

ግንቦት 28፣2016 - በኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች የሚረቡ በጎች ቆዳ፤ በጥራት እና ምቾቱ በገዥዎች ተመራጭ እንደሆነ ይጠቀሳል

በኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች የሚረቡ በጎች ቆዳ፤ በጥራት እና ምቾቱ በገዥዎች ተመራጭ እንደሆነ ይጠቀሳል።


ምቾቱ እና ጥራቱ በጎቹ ያሉበትን አካባቢ ቅዝቃዜ ለመቋቋም በሚያበቅሉት ወፍራም ጸጉር ውጤት እንደሆነ፤የቆዳ ውጤቶችን የሚያመርተው ‘’ኮትኬት ትሬዲንግ’’ የተባለው ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ታደሠ ነግረውናል።


በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስለሺ ለማም፤የደጋ በጎች ቆዳ ኢትዮጵያን ከተቀረው አለም ከሚለዩ ምርቶች አንዱ ነው ብለዋል።

ጥራቱ እና ምቾቱ ከፍተኛ፤ ተፈላጊነቱም እንዲህ የበዛ ከሆነው የደጋ በጎች ቆዳ ግን ኢትዮጵያ የሚገባትን ያህል እንዳልተጠቀመች ተነግሯል።



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page