top of page

ግንቦት 25 2017 - ኢትዮዽያ በሎጅስቲክስ ሥራ ዛሬም ከዓለም 167 ሀገሮች 126ተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች ተባለ።

  • sheger1021fm
  • Jun 2
  • 1 min read

በሎጅስቲክስ ማእዘን አራት ደረጃዎችን አሻሽላ ነው 126 ነች የተባለው።


ይህ የተሰማው ዛሬ የኢትዮዽያ ብሔራዊ ሎጅስቲክስ ባለሞያዎች ማህበር ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው ጋር በመከረበት ወቅት ነው።


የኢትዮዽያን ኢኮኖሚ ለማሳደግ በተለይ በሎጅስቲክስ ማእዘን ለውጥ እንዲመጣ እየተመከረ ነው ተብሏል።


የኢትዮዽያ የሎጅስቲክስ ኢንዱስትሪ ከፍ እንዲል አቅምና ተወዳዳሪነትን ለመፍጠር ፖሊሲዎችም እንዲሻሻሉ በማሰብ የጥናት ወረቀቶች ቀርበዋል።


በሎጅስቲክ ስራ ምርት ወይም አገልግሎትን በማደራጀት፤ በማሳደግ ከአገልግሎት አቅራቢዎች ወይም ከአምራቾች እስከ ደንበኛ ማጓጓዝ፤ ማስተላለፍ፣ ማሰራጨት ማቅረብ እና ማስተዳደር በኩል ኢትዮዽያ ዛሬም የምትፈተንበት እንደሆነ ተሰምቷል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……



ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page