top of page

ግንቦት 2፣2016 - የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ለኢትዮጵያ ምን ያስገኝላታል፤ ምንስ ያሳጣታል?

ኢትዮጵያ "በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት" መሰረት ከ5,800 በላይ የሌሎች ሀገራት ምርቶች ያለ ታሪፍ ወደ ገበያዋ ገብተው እንዲሸጡ ተስማምታለች።


ስጋ እና የስጋ ውጤቶችን ጨምሮ ደግሞ የ453 ምርቶችን የታሪፍ ከለላ ለተወሰነ ጊዜ አላነሳም ብላለች።


በ193 ምርቶች የታሪፍ ጉዳይ ምን ጊዜም አትምጡብኝ ማለቷንም ሠምተናል።


"የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት" ከስድስት ዓመት በፊት በጎርጎርሳውያኑ 2018 በአርባ አራት አገራት መፈረሙ ይታወሳል።


አሁን ላይ ይህንን ስምምነት ከሃምሳ አምስቱ የአፍሪካ አገራት 54 ፈርመውታል።


ያልፈረመችው ብቸኛ አገር ኤርትራ ናት ።


በአካውንቲንግና ህግ የተመረቁ የሌሎች አገራት ሞያተኞች ጭምር በአገሯ እንዲሰሩ ቃል የሰጠችበት ይህ ስምምነት ምን ያስገኝላታል፤ ምንስ ያሳጣታል?


ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page