top of page

ግንቦት 2፣2016 - አዲስ አበባ ላይ ቤት ማግኘት እየከበደም፣ ከአቅም በላይ እየሆነ መምጣቱ ይነገራል

አዲስ አበባ ላይ ቤት ማግኘት እየከበደም፣ ከአቅም በላይ እየሆነ መምጣቱ ይነገራል፡፡


በተለይም በወርሃዊ ደመወዝ ለሚተዳደር የከተሜው ሰው የአቅሙን ቤት ገዝቶ ለመኖር አሁን አሁን እንደ ጉም የማይጨበጥ ህልም እየሆነ መጥቷል ይባላል፡፡


በየጊዜው አዳዲስ የሪልስቴት ገንቢ ኩባንያዎች እየተበራከቱ ቢመጡም ትኩረታቸው አቅም ያለውን ማህበረሰብ እንጂ ወርሀዊ ደመወዝ ከፍሎ የሚኖረውን ሰራተኛ አይመለከቱም፡፡


ይህንን ክፍተት እሞላለሁ በማለት ከ9 ወር በፊት ስራዉን የጀመረው ኪ ፋይናንስ ሶሉሽን ለመጀመሪያ ጊዜ ባወጣሁት እጣ መሰረት ተመዝግበው ከነበሩ ቆጣቢዎች መካከል 58 የሚሆኑት የቤት ባለቤት እንዲሆኑ አድርጌያለሁ ብሏል፡፡


የ ተቋሙ ስራ አስኪያጅ አቶ ግሩም ይልማ አሁንም ትኩረታችን አቅም ኖሮት ቤት መግዛት በማይችለው ማህበረሰብ ነው ብለዋል፡፡


ተቋሙ ከአዲስ አበባ ሆቴልና ቱሪዝም ባለሞያዎች ማህበር ስምምነት ያደረገ ሲሆን ስምምነታቸውም የማህበሩ አባላት በ ኪ ሀውሲንግ በኩል እየቆጠቡ ቤት ለማግኘት ያለመ ነው፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page