top of page

ግንቦት 19፣2016 - በአዲስ አበባ በሚጀመረው የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ተቋማትና ማህበራት አጀንዳዎችን አደራጅተው እንዲገኙ ጥሪ ቀረበ

  • sheger1021fm
  • May 27, 2024
  • 1 min read

ከነገ በስትያ በአዲስ አበባ በሚጀመረው የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ተቋማትና ማህበራት አጀንዳዎችን አደራጅተው እንዲገኙ ጥሪ ቀረበ፡፡


ኮሚሽኑ ከመጭው ረቡዕ ጀምሮ ለተከታታይ 6 ቀናት በአዲስ አበባ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ስራ አከናውናለሁ ብሏል፡፡


በሃገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባት ሊፈጠረባቸው ይገባል የተባሉ የተመረጡ አጀንዳዎችንም ከማህበረሰቡ ባለፈ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትና ማህበራት አጀንዳ አደራጅተው ለማቅረብ እንዲዘጋጁ ኮሚሽኑ አሳስቧል፡፡


ከመጭው ግንቦት 21 እስከ 27 2016 በአዲስ አበባ ደረጃ በሚካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ የተለያዩ ሶስት ውጤቶችን እንጠብቃለን ብለዋል ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት ዋና ኮሚሽነሩ ፕ/ር መስፍን አርአያ፡፡


በዚህም የአጀንዳ ሀሳቦችን ከማሰባሰብና ከማደራጀት ባሻገር የአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ከባለደርሻ አካላት ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል፡፡


እንዲሁም የተለያዩ ጉዳዩ የሚያገባቸው አካላት ለሃገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮች የሚመረጡበትን መደላደል መፍጠርም ከውይይቱ የሚጠበቅ ነው ብለዋል ኮሚሽነሩ፡፡

በድሬደዋና በሌሎችም የተሳታፊዎች ልየታ በተካሄደባቸው 10 ክልሎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራው ይቀጥላል ተብሏል፡፡


በአማራና ትግራይ ክልሎች ግን የተሳታፊዎች ልየታ ሂደት ገና መሆኑን ኮሚሽኑ መናገሩ ይታሳል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page