top of page

ግንቦት 15 2017 - '' እንደ ሃገር ከዩኒቨርሲቲ የሚመረቁ ተማሪዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው''

  • sheger1021fm
  • May 23
  • 1 min read

በኢትዮጵያ አራት ሚሊዮን ተማሪዎችን ማሰልጠን የሚችሉ የቴክኒክና ሞያ ተቋማት እንዳሉ ይነገራል፡፡


በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር እያሽቆለቆለ በመምጣቱ ወደ ቴክኒክና ሞያ ትምህርት ቤት የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር እንዲጨምር አድርጎታል ተብሏል፡፡


አቶ ገላና ወ/ሚካኤል በኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ምክትል የቢሮ ሃላፊ ናቸው፡፡


እርሳቸው እንደሚሉት እንደ ሃገር ከዩኒቨርሲቲ የሚመረቁ ተማሪዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው ብለዋል፡፡


ሆኖም ከቴክኒክና ሞያ ተቋማት ሰልጥነው የሚወጡ ተማሪዎች አያስፈልጉም ማለት እንዳልሆነና የተሻለ የደመወዝ ተከፋይ እነሱ እንደሆኑ ነግረውናል፡፡



ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page