top of page

ግንቦት 14 2017 - አዋሽ ባንክ በ"አዋሽ ብር ፕሮ" መተግበሪያ የነዳጅ ክፍያ መክፈል መጀመሩን ተናገረ።

  • sheger1021fm
  • May 22, 2025
  • 1 min read

አዋሽ ባንክ በ"አዋሽ ብር ፕሮ" መተግበሪያ የነዳጅ ክፍያ መክፈል መጀመሩን ተናገረ።


ባንኩ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እንዲሁም ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ዲጂታል የነዳጅ ክፍያ ስርዓት ዛሬ ለገሀር በሚገኘው ራስ ሼል ማደያ በይፋ አስጀምሯል።


ይህ የአዋሽ ብር ፕሮ ዲጂታል የነዳጅ ክፍያን ለመፈጸም የሚያስችል ምቹ እና ቀላል መተግበሪያ መሆኑ ተነግሯል።


የአዋሽ ባንክ ደንበኞች ለመኪናዎቻቸው ለሚቀዱት ነዳጅ በአዋሽ ብር-ፕሮ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ በመጠቀም በኪው-አር ኮድ እንዲሁም የደንበኛውን ስልክ በመጠቀም በዩኤስኤስዲ (USSD) የደንበኛውን የይለፍ ቃል በማስገባት ብቻ ክፍያ መፈጸም የሚያስችል ነው ተብሎለታል።


ከዚህም በተጨማሪ ባንኩ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ከበዙ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በጋራ በመሥራት ላይ እንደሚገኝም አስረድቷል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page