top of page

ግንቦት  14፣2016 - በምስራቅ ወለጋ ባለፉት 2 ዓመታት፤ በአንድ ወረዳ ብቻ 556 መኖሪያ ቤቶች በታጣቂዎች ተቃጥለዋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • May 22, 2024
  • 1 min read

በምስራቅ ወለጋ ዞን ባለፉት 2 ዓመታት፤ በአንድ ወረዳ ብቻ 556 መኖሪያ ቤቶች በታጣቂዎች ተቃጥለዋል ተባለ፡፡

 

ከተቃጠሉት ውስጥም የሚበዙት የአማራ ተወላጆች የመኖሪያ ቤቶች መሆናቸው የተነገረ ሲሆን የኦሮሞ ተወላጆች ቤትም ተቃጥለዋል ተብሏል፡፡

 

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዲጋ በተባለ አንድ ወረዳ ብቻ በሁለት ዓመት ዉስጥ 3334 ሰዎችም በፀጥታ ችግር ምክንያት መፈናቀላቸው ተነግሯል፡፡

 

በወረዳው በአጠቃላይ 765 አባወራዎች መፈናቀላቸውና ከእነዚህ መካከልም 386 አባወራዎች  በእዚያው ዲጋ ወረዳ በኮምፕ ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል፡፡

 

ከ200 የሚበለጡ አባወራዎች ደግሞ  ከነቤተሰባቸው ወደ አማራ ክልል እንደሄዱም ተጠቁሟል፡፡

 

እነዚህ አባወራዎች የተፈናቀሉት፤ መልካ ቤቲ ጂቱ፣ በሬዳ ሶሮማ፣ አርጆ ቆቴቡላ እና ሰባተኛ ካምፕ ተብለው ከሚጠሩ  4 የወረዳው ቀበሌዎች መሆኑንም ሰምተናል፡፡

 

ይህንን ለሸገር የነገሩት በምስራቅ ወለጋ ዞን ዲጋ ወረዳ ቡሳ ጎኖፋ(አደጋ ስጋት ስራ አመራር) አስተባባሪ ወንድሙ ምትኩ ናቸው፡፡

በአሁን ወቅት በቦታው አንጻራዊ ሰላም እየታ ነው ያሉን አቶ ወንድሙ፤ ተፈናቃዎቹን ቀስ በቀስ ወደ ቀደመው ቀዬአቸው የመመለስ ስራ ተጀምሯል ብለውናል፡፡

 

ተፈናቅለው ከነበሩት የኦሮሞ ተወላጆች የሚበልጡት ወደ ቀደሞ ቤታቸው የተመለሱ ቢሆንም 120 አባውራዎች አሁንም ስጋት ስላለ አልተመለሱም ተብሏል፡፡

 

ቤታቸው ከተቃጠሉባቸው አባወራዎች መካከል ለ97ቱ መንግስት ቤት ሰርቶ እንዲገቡ አድርጓል ሲሉ አቶ ወንድሙ ተናግረዋል፡፡

 

እስከ ሰኔ 30 ድረስ የአማራ ተወላጆችንም ጨመሮ አሁን ያልተመለሱት የአሮሞ ተለወላጆችን ለመመለስ እቅድ ይዘን እየሰራን ነው ብለውናል፡፡

 

ይህ ማለት ግን አካባቢው ሰላም ሳይረጋገጥ ‘’በአንዴ ኑ ተመለሱ ይባላሉ’’ ማለት እንዳልሆነም ጠቁመዋል፡፡

 

እየተመለሱ ያሉ ተፈናቃዮችም ቢሆን ቤት ንብረታቸው ከመውደሙ በተጨማሪ፤ መሬታቸውን ሳያርሱ የቆዩ መሆናቸው ሌላው አሳሳቢ ችግር እንደሚሆንባቸው ተነግሯል፡፡

 

በዚህም የተነሳ ለተፈናቃዮች ረጂ አካላት የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘጉላቸው፤ የወረዳው መንግስት ጠይቋል፡፡

 

ሸገር ተፈናቃዮቹ ስላሉበት አጠቃለይ ሁኔታ እና ስለ አካባቢው ወቅታዊ የፅጥታ ሁኔታ የወረዳው አስተዳዳሪ መንግስቱ መገርሳን ጠይቆ ተከታዩን ምላሽ አግኝቷል፡፡ 

 

ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page