top of page

ግንቦት 10፣2016 - ዳሸን ባንክ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ሽልማት አንደተሰጠው ተናገረ

ዳሸን ባንክ የዓለም ባንክ አካል ከሆነው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ሽልማት አንደተሰጠው ተናገረ፡፡


ሽልማቱ የላቀ ዓለም አቀፍ የንግድ ፋይናንስ አገልግሎት በሚሰጡ ባንኮች ዘርፍ መሆኑን ባንኩ ለሸገር በላከው መግለጫ አስረድቷል፡፡


ለባንኩ ሽለማቱ የተሰጠው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) 8ኛ ዓለም አቀፍ ጉባኤውን በስፔን ባርሴሎና ባደረገበት ወቅት መሆኑ ተነግሯል፡፡


በተያያዘ ወሬ ዳሸን ባንክ በሀገሪቱ ለሚገኙ ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ተቋማት የፋይናንስ አገልግሎት የመስጠት አቅሙን ይበልጥ ለማሳደግና የፋይናንስ ተደራሽነትን በተሻለ ሁኔታ ለማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ከኮርፖሬሽኑ ጋር ተፈራርሟል፡፡

ስምምነቱን ሩዋንዳ ኪጋሊ ተገኝተው የፈረሙት የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው አለሙ ናቸው፡፡


ስምምነቱ ዳሸን ባንክ የፋይናንስ ተደራሽነትን እና አካታችነትን ይበልጥ እውን ለማድረግ አቅም የሚጨምርለት መሆኑ ተነግሯል፡፡


የተደረገው ሰምምነት በጥቃቅን፣አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም በግብርና ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች በተለይ በሴት ባለቤትነት የሚመሩትን ይበልጥ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎለታል።



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page