top of page

ግንቦት 1 2017 - የት/ት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፤ ከግንቦት 18 2017 ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያ የሌለውን አላስተናግድም አለ

  • sheger1021fm
  • May 9
  • 1 min read

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፤ ለምሰጣቸው አገልግሎቶች ከግንቦት 18 ቀን 2017 ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያ የሌለውን አላስተናግድም አለ፡፡


የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ወደ ተቋሙ የትምህርት መረጃ ድጋሜ ለመውሰድና ለማጣራት፣ ለማረጋገጥ፣ የትምህርት ማስረጃችሁን ለማስላክ፣ ስም ላይ የፊደላት ግድፈትን ለማስተካከልም ከፈለጋችሁ ፋይዳ መታወቂያ ይዛችሁ ኑ ተብላችኋል፡፡


በተጨማሪም የድጋፍ ደብዳቤ ለማጸፍ ለሚፈልግ ማንኛውም ተገልጋይ ከግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያ ቁጥር የግዴታ አስፈላጊ እንደሆነ ከሲቪል ምዝገባና ከነዋሪዎች አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page