top of page

ግንቦት 1፣2016 - በአዲስ አበባ የግልና የመንግስት ተቋማት አካባቢ እየበከሉ ነው ተባለ

  • sheger1021fm
  • May 9, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ የግልና የመንግስት ተቋማት አካባቢ እየበከሉ ነው ተባለ፡፡


ከግለሰቦች ቤት የሚወጡ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻም ብክለቱን እያባባሰው መሆኑን ሰምተናል፡፡


ሁሉም የራሴ በሚልባት አዲስ አበባ፤ ኢንዱስትሪው፣ ሪልስቴቶች እንዲሁም የተለያዩ ህንፃዎች ሲገነቡ ፍሳሻቸውን አከማችተው የሚያስመጥጡበት መንገድ የላቸውም ተብሏል፡፡


ኢንዱስትሪዎች ሲገነቡ ማህበረሰቡ ላይ ምን ጉዳት ያመጣሉ የሚለው ሳይሆን የሚታየው የሚያስገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ብቻ እንደሆነ ተነግሯል፡፡


እነዚህ ተቋማት እንዲገነቡ ፍቃድ የሚሰጠውም አካልም ተቋማቱ ሲገነቡ ማስቀደም ያለባቸው ምን አይነት ጉዳት ያስከትላሉ የሚለውን ትኩርት መስጠት ይኖርበታልም ተብሏል፡፡


የአዲስ አባባ ከተማ አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፤ በበኩሉ የብክለት ቁጥጥርን ለማስተካከል ከ13,000 በላይ በሆኑ ተቋማት ላይ ክትትል አድርጌ በ2250ዎቹ ላይ እርምጃ ወስጄባቸዋል ብሏል፡፡


ከተለያዩ ተቋማት እንዲሁም ከመኖሪያ ቤቶች የሚለቀቁ ደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻዎች፤ መልሰው የምንመገባቸው ምግቦች ሳይቀር እየበከሉ ነው መባሉንም ሰምተናል፡፡


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page