top of page

የፖለቲካ ፓርቲዎች የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ።

  • May 21
  • 1 min read

ግንቦት 13/2018


የፖለቲካ ፓርቲዎች የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ።


ከ10 ቀናት በኋላ የሚካሄደው ሃገር አቀፍ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ሃገራዊ ሰላምን ለማፅናት በሚል የፊታችን እሁድ የአደባባይ የፀሎት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተናግሯል።


የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች በወሰኑት መሰረት የፊታችን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው አራዳ ፓርክ ሃገር አቀፍ የፀሎት መርሃ ግብር መሰናዳቱን የጉባኤው  ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ በጉዳዩ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰዋል።



ቀሲስ ታጋይ የፀሎት መርሃ ግብሩን አላማዎች ሲጠቅሱም በሃገር ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማገዝ  ምዕመናን ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ፤ የፓለቲካ ፓርቲዎችም የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ ለመጠየቅ፤ እንዲሁም ብሄራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና ሰላምን ለማምጣት የፈጣሪ እገዛን ለመጠየቅ የሚደረግ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡


ከዛሬ ጀምሮ ማህበራዊ ሚዲያን ጨምሮ በመገናኛ ብዙሃን አጭር የሰላም መልዕክቶች ይተላለፋሉ፤ ከነገ ጀምሮ ደግሞ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር በእጅ ስልኮች ተመሳሳይ መልዕክቶች ይተላለፋሉ፤ እሁድ በሚኖረው የአደባባይ ፀሎት ከሁሉም ቤተ እምነት የተወጣጡ ከ1000 በላይ ሰዎች ይገኛሉ ተብሏል፡፡


በመርሃ-ግብሩ የሃይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች፣ የምርጫ ቦርድና የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ይገኛሉ፡፡


የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤው በክልሎች ባለው መዋቅር በተመሳሳይ ሰዓት በሁሉም ክልሎች የአደባባይ ፀሎቱ ይካሄዳል መባሉን ሰምተናል፡፡

 

ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page