top of page

የጥቅምት 8፣2017 የአፍሪካ መሪዎች ከአሁኑ ቴክኖሎጂን ተከትለው በሚመጡ ጉዳዮች ዙሪያ ህግ ሊያበጁ እና ሊዘጋጁ ይገባል ተባለ

መጪው ጊዜ ለአፍሪካ መሪዎች ፈታኝ ስለሚሆን ከአሁኑ ቴክኖሎጂን ተከትለው በሚመጡ ጉዳዮች ዙሪያ ህግ ሊያበጁ እና ሊዘጋጁ ይገባል ተባለ፡፡


ዘመኑ የሚያፈራቸው የቴክኖሎጂ ግኝቶች ከሰብአዊ መብትም ሆነ ከአስተዳደር አንፃር ለመሪዎች ፈተና ሊሆን ስለሚችል በተለይም የአፍሪካ መሪዎች መጪውን ጊዜ በማሰብና ህግ በማውጣት መዘጋጀት ይኖርባቸዋል ተብሏል፡፡


የፓን አፍሪካ የጠበቆች ማህራት ህብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲደረግ እንደሰማነው አንዱና የአፍሪካ መሪዎቸን ወደፊት ሊፈትን የሚችለው ጉዳይ አርተፊሻል ኢንተለጀንስ በመሆኑ ከጥቅሙ ባልተናነሰ ወይም በበለጠ መልኩ ችግር ይዞ ሊመጣ ይችላል ተብሏል፡፡


ለዚህም ከወዲሁ የህግ ማዕቀፍ ማበጀት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ለሸገር ሬዲዮ የተናገሩት አፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት ምክትል ፕሬዘዳንትና የፌዴራል የጠበቆች ማህበራት ፕሬዘዳንት የየሆኑት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ናቸው፡፡




የኔነህ ሲሳይ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page