top of page

የጥቅምት 8፣2017 - ‘’አክሱም ወደ ሰላሟ ብትመለስም እንደቀድሞው ጎብኚዎች እየመጡ አይደለም’’ የአክሱም ከተማ ሆቴል ባለንብረቶች ማህበር

  • sheger1021fm
  • Oct 18, 2024
  • 1 min read

‘’አክሱም ከተማ ወደ ሰላሟ ብትመለስም እንደቀድሞው ጎብኚዎች እየመጡ አይደለም’’ ሲል የአክሱም ከተማ ሆቴል ባለንብረቶች ማህበር ተናገረ፡፡


‘’ከተማው ውስጥ አሁን ሙሉ ለሙሉ ሰላም ሰፍኗል’’ የሚለው ማህበሩ እየመጡ ያሉ ጎብኚዎች ቁጥር ግን አነስተኛ ነው ብሏል፡፡


የአክሱም ከተማ የሆቴል ባለንብረቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ጎይቶም ትዕዛዙ ‘’ከሰሜኑ ጦርነት በፊት #አክሱም ከፍተኛ የሆነ የቱሪስት ፍሰት የነበረባት ስፍራ ነበረች’’ ብለዋል፡፡


‘’በጦርነቱ ምክንያት የቱሪስቶች ፍሰቱ ቆሞ ነበር የተባለ ሲሆን አሁን ባለው የሰላም ሁኔታ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ወደ አክሱም እያቀኑ ቢሆንም ቁጥራቸው ግን እጅ አነስተኛ ነው’’ ሲሉ ነግረውናል፡፡


#የቱሪዝም ባለሞያውና የሰለብሪቲ ኢትዮጵያ አስጎብኚ ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ካሣ ወደ አክሱም ጥናት ለማድረግ መጓዛቸው ነግረውናል፡፡


‘’አሁን ላይ አክሱም ሙሉ ለሙሉ ሰላም ሆናለች’’ የሚሉት አቶ አሸናፊ ከተማው ‘’ለቱሪስቶች እራሷን ዝግጁ አድርጋለች እየጠበቀች ነው ጎብኚዎች ወደ አክሱም ሊሄዱ ይገባል’’ ብለዋል፡፡



አቶ አሸናፊ ‘’አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እራሳቸውን በሚገባ እያዘጋጁ መሆኑን ታዝቤያለሁ’’ ያሉ ሲሆን ‘’ነገር ግን ግብአት አቅርቦት ላይ እጥረት አለ በተለይም እንደ ሱፐርማርኬት ያሉ ተቋማት ላይ እጥረት ይታያል በዚህ ዙሪያ ሊሰራ ይገባል’’ በማለት አሳስበዋል፡፡


የአክሱም ከተማ የሆቴል ባለንብረቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ጎይቶም ትእዛዙ በበኩላቸው ከጦርነቱ በኋላ ሆቴሎች ወደ ስራ ለመግባት የቻሉትን ያህል ዝግጅት እያደረጉ ቢሆንም የተማረ የሰው ሃይል እጥረት ግን እየገጠማቸው ነው በማለት ነግረውናል፡፡


መንግስትም ሆነ ባለድርሻ አካላት ይህንን ቢያደርጉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የበለጠ ጠንክረው ይሰራሉ ሲሉ ፕሬዘዳንቱ አሳሰበዋል፡፡


በረከት አካሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page