top of page

የጥቅምት 7፣2017 - ጡረተኞች እና የመንግስት ሰራተኞች የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ

ጡረተኞች እና የመንግስት ሰራተኞች የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ፡፡


በተለይ ጡረተኞች ቅሬታ ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በተደጋጋሚ ጊዜ ጡረተኞች እኛም ገቢያችን ዝቅተኛ በመሆኑ ተጠቃሚ እንሁን ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡


ይሁን እና በተያዘው የበጀት ዓመት እንዲመዘገብ እንቅስቃሴ መጀመሩን ከአዲስ አበባ ከተማ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ሰምተናል፡፡


ይህ በእንዲህ እንዳለ የጤና መድህን ተጠቃሚ ሆነን መድኃኒት ለመግዛት ወደ ከነማ መድኃኒት ቤቶች ስንሄድ መድኃኒት እያለ የለም እንባላለን ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታ ያነሳሉ፡፡


የከነማ መድኃኒት ቤቶች ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሀና ለካሳ እንዲህ አይነቱ የድርጅቱ ሰራተኛ ላይ እርምጃ እየወሰድነው ብለዋል፡፡



ማርታ በቀለ



Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page