የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ።
- May 21
- 1 min read
ግንቦት 13/2018
የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ።
ለተፈጠረው ችግር መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክ ወደ ስፍራው በቅርብ እንደሚያቀና ሚኒስቴሩ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው በሳምንቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን አካቷል፡፡

መግለጫውን የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ናቸው።
ቃል አቀባዩ በቅርቡ የተከናወኑ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በቅርቡ በህንድ በተካሄደው የብሪክስ አባላት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በደቡብ አፍሪካ ጥቃት ስለደረሰባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ ከአቻችው ጋር መወያየታቸውን አስረድተዋል።
በዚህም ወይይት ላይ ሁለቱ የስራ ሃላፊነት በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እየደረሱ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት መነጋገራቸው ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርሃኑ ጸጋዬ በኢትዮጵያ የሚገኙትን የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኖንሴባ ሎሲ ጋር በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ አስጠርተው ማነጋገራቸውን ከቃል አቀባዩ ሰምተናል፡፡
በውይይታቸውም የሀገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የደረሰውን ችግር መርምሮ በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል መግባቱን አምባሳደር ነብያት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ የሚከታተል እና የጋራ መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክም ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚላክ አክለው ጠቅሰዋል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments