የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት አዋሽ፣ የሪፍት ቫሊ ስምጥ ሸለቆና የኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የጎርፍ መከላከል ሥራዎች 170 ሺህ ነዋሪዎችን ከመፈናቀል አድኛለሁ አለ።
- Feb 26
- 1 min read
የካቲት 19/2018
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት በተደጋጋሚ ጎርፍ ሲያጠቃቸው በነበሩ አዋሽ፣ የሪፍት ቫሊ ስምጥ ሸለቆና የኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ ባለፉት አመታት በሰራኋቸው የጎርፍ መከላከል ሥራዎች 170 ሺህ ነዋሪዎችን ከመፈናቀል አድኛለሁ አለ።
ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በዚህ ሥራ 30 ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬትን ከጎርፍ መከላከል ችያለሁ ብሏል።
ይህ የተባለው የውሃና ኢነርጂ ሚንስትር ኤስ ደብሊው ኤስ (SWS) ከተባለ የጎርፍ መከላከል አማካሪ ድርጅት ጋር በመሆን የሰሩትን የኦሞ ጊቤ የተፋሰስ ልማት የተግባራዊነት የጥናት ግኝት ሪፖርት ላይ እየመከሩበት ባለ መድረክ ላይ ነው።

በመድረኩ የውሃ እና ኢነርጂ ሚንስትሩ ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ጥናቱ በተሰራባቸው ተፋሰሶች ተደጋጋሚ የጎርፍ አደጋ እየተከሰተ ሰዎችን ከመኖሪያ ቦታቸው ከማፈናቀል ጀምሮ ብዙ የሃብት ውድመት ሲያስከትል ነበር ብለዋል።
ይህንንም ተደጋጋሚ አደጋ ለማስቀረት እንዲህ ዓይነት ጥናቶች ተሰርተው ዘላቂ መፍትሄዎችን ማምጣት አስፈላጊ መሆኑን ሚንስትሩ ተናግረዋል።
በውሃ እና ኢነርጂ ሚንስትር የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ተስፋዬ አባቡ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ሲሰራ የነበረው የጎርፍ መከላከል ሥራ በአስቸኳይ ጊዜ አሰራርና በተመረጡ ቦታዎች ብቻ ነበር ያሉ ሲሆን ይህ ጥናት ግን ችግሩን በዘላቂነት ለማስቀረት የሚረዳ ነው ብለዋል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአጋር ተቋማት ጋር ያስጠናው የኦሞ ጊቤ የተፋሰስ ልማት የተግባራዊነት የጥናት ግኝት፤ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ምሁራንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሐዋሳ ከተማ በተዘጋጀው መድረክ ላይ እየመከሩበት ነው።
ንጋት መኮንን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments