top of page

የካቲት 7፣2016 - የህክምና ባለሞያዎች የሞያ ስነ-ምግባሩን ተከትለው ታካሚዎቻቸውን አለማስተናገዳቸው

በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ላይ ከሚነሱ ቅሬታዎች አንዳንድ የህክምና ባለሞያዎች ታካሚዎቻቸውን የሞያ ስነ-ምግባሩን ተከትለው አለማስተናገዳቸው ይጠቀሳል፡፡


ወደ ህክምና ተቋማት አገልግሎት ፈልጎ የሚሄድ ታካሚን በአግባቡና ሙያው በሚፈቅደው ልክ አገልግሎት መስጠት የተገባ ቢሆንም ይህ ሳይሆን ቀርቶ ስህተት የሚከሰትባቸው አጋጣሚዎች የታካሚዎችን ህይወት እስከመንጠቅ ይደርሳሉ፡፡


በተለይ ከጤና ባለሞያዎች ስርዓተ ትምህርት ጋር በተያያዘ የሚነሱትን ቅሬታዎች ለማስተካከልና ብቁ ባለሞያዎችን ለማፍራት ወደ ስራ ከመግባታቸውም በፊት የብቃት ምዘና ፈተና መስጠት፤ በስራ ላይ ያሉትም የሞያ ፈቃዳቸውን ለማደስ ተከታታይ የሞያ ማጎልበቻ ስልጠና መውሰዳቸውን የማረጋገጥ ስራ እየከወነ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡


ምህረት ስዩም



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page