ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲኖራት ያግዛል የተባለው የሽግግር ፍትህ በአግባቡ እንዲተገበር በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ እልባት መስጠት ይገባል ተባለ፡፡
ውጤታማ የሽግግር ፍትህ ለማካሄድ አንፃራዊ መረጋጋትና ሰላም ያስፈልጋል ተብሏል፡፡
የሽግግር ፍትህ ረቂቅ ፖሊሲን ያሰናዳው የባለሙያዎች ቡድን ሰነዱን ጥንቅቅ አድርጎ ለመንግስት ማስረከቡን መነገሩም ይታወሳል፡፡
ቀሪው ስራ ፖሊሲውን አፅድቆ ወደ ስራ መግባት መሆኑን የነገሩን ረቂቅ ፐሊሲውን ካሰናዱት የህግ ባለሞያዎች መካከል የሆኑት ዶ/ር ማርሸት ታደሰ ለተግባራዊነቱ ግን ሰላም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ለዚሁም መንግስትን ጨምሮ በግጭት አውድ ውስጥ ያሉ አካላት ሁሉ ችግሮችን በሰላም ለመፍታት ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments