top of page

የካቲት 6፣2016 - የሽግግር ፍትህ በአግባቡ እንዲተገበር ያሉ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ እልባት መስጠት ይገባል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Feb 14, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲኖራት ያግዛል የተባለው የሽግግር ፍትህ በአግባቡ እንዲተገበር በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ እልባት መስጠት ይገባል ተባለ፡፡


ውጤታማ የሽግግር ፍትህ ለማካሄድ አንፃራዊ መረጋጋትና ሰላም ያስፈልጋል ተብሏል፡፡


የሽግግር ፍትህ ረቂቅ ፖሊሲን ያሰናዳው የባለሙያዎች ቡድን ሰነዱን ጥንቅቅ አድርጎ ለመንግስት ማስረከቡን መነገሩም ይታወሳል፡፡


ቀሪው ስራ ፖሊሲውን አፅድቆ ወደ ስራ መግባት መሆኑን የነገሩን ረቂቅ ፐሊሲውን ካሰናዱት የህግ ባለሞያዎች መካከል የሆኑት ዶ/ር ማርሸት ታደሰ ለተግባራዊነቱ ግን ሰላም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡


ለዚሁም መንግስትን ጨምሮ በግጭት አውድ ውስጥ ያሉ አካላት ሁሉ ችግሮችን በሰላም ለመፍታት ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page