በኢትዮጵያ 6 ሚሊዮን ያህል ሰዎች የሚጥል ህመም ቢኖርባቸውም በቂ የህክምና አገልግሎት ባለመግኘትና ሌሎች ተደራራቢ ችግሮች ምክንያት የሚደርስባቸው ጫና የበረታ ነው ተባለ፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ የሚታሰበው የሚጥል ቀን አስመልክቶ ካልሆነ በቀር በጤና ዘርፉ ህመሙ በቂ ትኩረት አልተሰጠውም ተብሏል፡፡
ከሚጥል ህመም(ኢፕሊፕሲ) ጋር ተያይዞ ያለው የማህበረሰብ እውቀት ዝቅተኛ በመሆኑ ህክምና ለማግኘትም ይሁን በህመሙ የተያዘው ሰው በትምህርትና በሌሎች ማህበራዊ ህይወቱ ላይ የሚገጥሙት ፈተናዎች የበዙ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ዶ/ር ሕይወት ሰለሞን ስለ ሚጥል ህመም በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት ላይ ያለው ግንዛቤ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሚጥል ህመም ህክምና በተለያዩ ተቋማት በተለይ በመድሃኒት የሚሰጥ መሆኑን የኢትዮጵያ የነርቭ ሀኪሞች ማህበር ፕሬዘዳንት ዶ/ር ህሊና ዳኛቸው ነግረውናል፡፡
ምህረት ስዩም
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
コメント