top of page

የካቲት 6፣2016 - በአዲስ አበባ ከፊታችን አርብ እስከ የሚመጣው ሰኞ ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር አይቻልም ተባለ

በአዲስ አበባ ከተማ ከየካቲት 8 ቀን ጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት 2 ሰዓት ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር መከልከሉን የተናገረው የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ ነው፡፡


ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን የማያካትት ሲሆን፤ የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ሰኞ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ቢሮው አስረድቷል፡፡


ይህንን መልዕክት በሚተላለፉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሳደል ሲል ቢሮው አሳስቧል፡፡


ክልከላው የተጣለበትን ምክንያት ቢሮው አላስረዳም፡፡


በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page