top of page

የካቲት 5፣2016 - ስለተፈረመው ሰነድ ሆነ ሌሎች የኢትዮጵያን አቋም ስለሚመለከቱ ጉዳዮች ለአለም የማሳወቅ ስራ

ከሶማሌላንድ ጋር ስለተፈረመው የመግባቢያ ሰነድም ሆነ ሌሎች የኢትዮጵያን አቋም ስለሚመለከቱ ጉዳዮች ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የማሳወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የውጪ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናገረ፡፡


የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ፈቲ ማህዲ ቋሚ ኮሚቴው ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ኢትዮጵያ፣ በህዳሴ ግድቡ ላይ ስላላት አቋም፣ በሱማሌላንድና በኢትዮጵያ መካከል ስለተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ ምንነት፣ እንዲሁም ስለፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አተገባበርን በተመለከተ በ’’ፓርላሜንታዊ የዲፕሎማሲ’’ ዘርፍ እንዲያውቁ እየተደረገ መሆኑን ነግረውናል፡፡


በተጨማሪም በትግራይ ክልል ስለተከሰተው ድርቅ፣ ስለ ተሀድሶ ኮሚሽን እንዲሁም ሀገራዊ መግባባት ላይ ለመድረስ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እየሰራቸው ስላሉ ስራዎች ማብራሪያ እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡


ቋሚ ኮሚቴው ዛሬም ከጀርመን መንግስት ከተወከሉ የፓርላማ አባላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page