የካቲት 4 2017 - ''በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ከ15,000 በላይ እንግዶች ይሳተፋበታል ተብሎ ይጠበቃል'' የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
- sheger1021fm
- Feb 11
- 1 min read
የፊታችን ቅዳሜ አና እሁድ የሚካሄደውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ከ15,000 በላይ እንግዶች ይሳተፋበታል ተብሎ ይጠበቃል ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተናገረ።
ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን 35 የፌደራል ተቋማት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ያሉበት ዐብይ ኮሚቴ እና ንዑሳን ኮሚቴዎች ተቋቁመው በየጊዜው በመገምገግም ስራውን በውጤታማነት መርተዋል ተብሏል።

የጉባኤው ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ከስብሰባውም በተጨማሪ #የቱሪስት_መዳረሻዎችን እንዲጎበኙ፣ የልማት ጥረቶችንና ውጤቶችን ተዟዙረው እንዲያዩ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች እንዲቋደሱና እንዲገበያዩ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃል ሲል አገልግሎቱ አስታውሷል።
ለዚህም "እንግዶችን ተቀብለን በምናስተናግድበት ወቅት እንደ ሙያ ዘርፋችን ብቻ ሳይሆን እንደ አንድ እንግዳ ተቀባይ ኢትዮጵያዊ መሆን አለበት" ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስረድቷል።
コメント