top of page

የካቲት 4 2017 - በአዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ፊታችን እሁድ ምሽት ድረስ የሞተር ሳይክል ማሽከርከር ተከለከለ

  • sheger1021fm
  • Feb 11
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ፊታችን እሁድ ምሽት ድረስ የሞተር ሳይክል ማሽከርከር ተከለከለ፡፡


በመዲናችን የሚካሄደው #የአፍሪካ_መሪዎች_ጉባኤ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ተከልክሏል ሲል የከተማዋ የትራንስፖርት ቢሮ ተናግሯ።



ስለሆነም ከዛሬ የካቲት 04/2017 ዓ.ም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 09/2017 ዓ.ም ድረስ በመዲናዋ በየትኛውም አካባቢ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር እንደማይቻል ቢሮው አሳውቋል።


በተያያዘ ወሬ በአዲስ አበባ የሚካሄደውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ማንኛውም ተሽከርካሪዎች በ #ኮሪደር_ልማት በለሙና የእንግዶች መተላለፊያ በሆኑ መንገዶች ላይ መቆም እንደማይችሉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ማሳሰቡ ይታወሳል፡፡


ከዛሬ የካቲት 04/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ዓለም አገራት እንግዶች የሚገቡ በመሆኑ እስከ የካቲት 09/2017 ዓ.ም ማታ 12:00 ድረስ በኮሪደር በለሙ መንገዶች ላይ ተሽከርካሪዎች መቆም አይችሉም ተብሏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page