በሕወሃት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በንግግር ለመፍታት የአሜሪካና የእንግሊዝ ባለስልጣናትን ጨምሮ የተለያዩ ዲፕሎማቶች መቀሌ መግባታቸው ተሰማ፡፡
በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው መረጃ አምባሳደሮች፣ የአሜሪካ ኤምባሲ ከፍተኛ ዲፕሎማት ተወካዮች፣ ከአውሮፓ ህብረት፣ ከፈረንሳይ፣ ከጣሊያን እና ከእንግሊዝም የተውጣጡ ዲፕሎማቶች መቀሌ ገብተዋል፡፡

ዲፕሎማቶቹ ከጌታቸው ረዳ እና ከሕወሃት ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል ጋር እንደሚነጋገሩ ተሰምቷል፡፡
ዲፕሎማቶቹ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ከተፈናቃዮች ተወካዮች ጋርም ተገናኝተው እንደሚወያዩ ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያሳያ፡፡
በህወሃት ባለስልጣናት መካከል የተፈጠረው መከፋፈልና አለመግባባት ለአንድ ከተማ ሁለት ከንቲባ እስከመሾም የደረሰ በመሆኑና በዚህም በተፈጠረው ሽኩቻ ህብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት መቸገሩን በሰላማዊ ሰልፍ ጭምር መግለፁ ይታወሳል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5rs
Comments