top of page

የካቲት 4 2017 - በሕወሃት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በንግግር ለመፍታት ዲፕሎማቶች መቀሌ መግባታቸው ተሰማ

  • Feb 11, 2025
  • 1 min read

በሕወሃት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በንግግር ለመፍታት የአሜሪካና የእንግሊዝ ባለስልጣናትን ጨምሮ የተለያዩ ዲፕሎማቶች መቀሌ መግባታቸው ተሰማ፡፡


በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው መረጃ አምባሳደሮች፣ የአሜሪካ ኤምባሲ ከፍተኛ ዲፕሎማት ተወካዮች፣ ከአውሮፓ ህብረት፣ ከፈረንሳይ፣ ከጣሊያን እና ከእንግሊዝም የተውጣጡ ዲፕሎማቶች መቀሌ ገብተዋል፡፡

ዲፕሎማቶቹ ከጌታቸው ረዳ እና ከሕወሃት ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል ጋር እንደሚነጋገሩ ተሰምቷል፡፡


ዲፕሎማቶቹ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ከተፈናቃዮች ተወካዮች ጋርም ተገናኝተው እንደሚወያዩ ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያሳያ፡፡


በህወሃት ባለስልጣናት መካከል የተፈጠረው መከፋፈልና አለመግባባት ለአንድ ከተማ ሁለት ከንቲባ እስከመሾም የደረሰ በመሆኑና በዚህም በተፈጠረው ሽኩቻ ህብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት መቸገሩን በሰላማዊ ሰልፍ ጭምር መግለፁ ይታወሳል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን



📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page