top of page

የካቲት 28፣2016 - የአሸጎዳ ነፋስ ሃይል ማመንጫ ከሶስት ዓመት በኋላ ዳግም ስራ መጀመሩ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Mar 7, 2024
  • 1 min read

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ስራ አቆሞ የነበረው እና በትግራይ ክልል የሚገኘው የአሸጎዳ ነፋስ ሃይል ማመንጫ ከሶስት ዓመት በኋላ ዳግም ስራ መጀመሩ ተነገረ።


በትግራይ ክልል የሚገኘው አሸጎዳ የነፋስ ሃይል ማመንጫ ስራ የጀመረው 2006 ላይ ነበር።


በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ግን የነፋስ ሃይል ማመንጫው ለሶስት አመታት ስራ አቆሞ እንደቆየ፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ነግረውናል።


በጦርነቱ ምክንያት ለሃይል ማመንጫው ተገቢውን ጥገና ማድረግ ባለመቻሉ ስራ አቁሞ ቆይቷል ብለዋል።


ንጋቱ ረጋሣ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page