የካቲት 27 2017 -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ግብር ያልከፈሉትን ደንበኞቹን ከሀገር እንዳይወጡ አገደ።
- sheger1021fm
- Mar 6
- 1 min read
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ግብር ያልከፈሉትን ደንበኞቹን ከሀገር እንዳይወጡ አገደ።
ከ3.2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉም ተሰምቷል።
ቢሮው የሚገባኝን ከ3.2 ቢሊዮን ብር በላይ የግብር ዕዳ ያለባቸውን ደንበኞች በተደጋጋሚ ጥሪ ባደርግም ዕዳቸውን ለመክፈል ፈቃደኛ አልሆኑም ብሏል።
እነዚህ 62 ግለሰቦች በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዝርዝራቸውን አስተላልፏል ተብሏል።

ቢሮው በ2017 በጀት ዓመት የግብር ዕዳቸውን የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በአግባቡ በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በአዲስ መልክ አደራጅቻለሁ ብሏል፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት ከ6.4 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ መሰብሰቡን ተናግሯል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r
Σχόλια