top of page

የካቲት 26 2017 - ለጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የንግድ ስራ የሚሆን የሞባይል መተግበርያ መልማቱ ተነገረ

  • Mar 5, 2025
  • 1 min read

ለጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የንግድ ስራ ማቀላጣፊያነት የሚሆን የሞባይል መተግበርያ መልማቱ ተነገረ፡፡

 

መተግበርያውን አልምቶ ወደ ስራ  ያስገባው ብሩህ ማይንድስ ኮንሰልት የተሰኘ ተቋም ነው፡፡

'መንሽ' የሚል መጠሪያ ያለው ይህ መተግበርያ አሁን ላይ በሁለት ቋንቋ (በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ) አገልግሎት እንደሚሰጥ እና በሌሎች ቋንቋዎች ደግሞ በቅርቡ እንደሚጀምር ተነግሯል፡፡

 

ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊትና ከገቡም በኋላ የስልጠና እና የምክር አገልግሎችን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ያገኛሉ ተብሏል፡፡

 

አገልግሎቱን ሲጠቀሙ የነፃና የክፍያ አገልግሎቶች እንዳሉት ሰምተናል፡፡

በተለይ ለስራ ጀማሪዎች እና አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በባለሞያ ምክር በስልጠና ወቅታዊ የገበያ መረጃ እንዲሁም መነሻ አነስተኛ ብድር አገልግሎቶችን ከተለያዩ የገንዘብ ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ተነግሯል፡፡

 

የንግድ ስርዓአት በተበታተነና ደረጃውን ባልጠበቀ መልኩ በልገሳ ሲተገበር በመቆየቱ ዘርፉ ትርጉምያለው ውጤት እንዳያመጣ አድርጎታልም ተበሏል፡፡

 

በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታተት ይህ መንሽ የተሰኘ መተግበራያ ግሩም መላ ሲባልለት ሰምተናል፡፡

 

መንሽ መተግበሪያን  ከፕለይ እስቶር እና አፕ እስቶር በማውረድ የንግድ ስራ አገልግሎቶችን እና የገበያ ትስስሮችን ማግኘት ይቻላል ተብሏል፡፡

 

መንሽ መተግበሪያን ያበለፀገው ብሩህማይንድስ ኮንሰልት ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ብቻ ከ27ሺ በላይ ወጣቶችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ማሰማራቱን ሰምተናል፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

 

Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page