top of page

የካቲት 25፣2016 - የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ከዛሬ ጀምሮ በዘመቻ ይሰጣል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Mar 4, 2024
  • 1 min read

የማህፀን በር ካንሰር በሽታ መከላከያ ክትባት ከዛሬ ጀምሮ በዘመቻ ይሰጣል ተባለ፡፡

ይህን ያለው የጤና ሚኒስቴር ነው፡፡


ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ በኢትዮጵያ በዓመት በማህጸን በር ካንሰር ምክንያት ከ5 ሺህ በላይ ሴቶች ህይወታቸው ያጣሉ ብለዋል፡፡


እንዲሁም እድሜያቸው ከ14 ዓመት በላይ ከሆኑት ሴቶች ከአምስቱ አራቱ በህይወት ዘመናቸው ለማህፀን በር ካንሰር ተጋላጭ እንደሚሆኑም ተናግረዋል፡፡


የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ከ2011 ዓ.ም እስከ አሁን ባሉት ጊዜያት በዓመት 2 ጊዜ በ6 ወር ልዩነት ሁለት ዶዝ ክትባት ሲሰጥ መቆየቱን ሚኒስትሯ አስታውሰዋል፡፡


አለማቀፍ ጥናቶች መሰረት በማድረግ አንድ ጊዜ በተከተቡት እና ሁለት ጊዜ በተከተቡት ልጆች መካከል የክትባቱ ውጤታማነት ሲታይ ተመጣጣኝ የሚባል የመከላከል አቅም በማሳየቱ፣ ከዚህ ዓመት ጀምሮ አንድ ዶዝ ብቻ ይሰጣል ብለዋል፡፡



በ2016 ዓ.ም 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜያችው 14 ዓመት የሆናቸው ሴቶች ልጆች ለመከተብ ታቅዷል ተብሏል።


ክትባቱ በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ተቋማት፣ በግዝያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎችም እንደሚሰጥ ሰምተናል።


ወላጆች ወይም አሳዳጊዎች እድሜያቸው 14 ዓመት የሆናቸው ሴት ልጆች የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት እንዲወስዱ በማድረግ ግዴታቸውን እንዲወጡም በጤና ሚኒስቴር ጥሪ ቀርቧል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comentarii


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page