top of page

የካቲት 25፣2016 - የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ከዛሬ ጀምሮ በዘመቻ ይሰጣል ተባለ

  • Mar 4, 2024
  • 1 min read

የማህፀን በር ካንሰር በሽታ መከላከያ ክትባት ከዛሬ ጀምሮ በዘመቻ ይሰጣል ተባለ፡፡

ይህን ያለው የጤና ሚኒስቴር ነው፡፡


ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ በኢትዮጵያ በዓመት በማህጸን በር ካንሰር ምክንያት ከ5 ሺህ በላይ ሴቶች ህይወታቸው ያጣሉ ብለዋል፡፡


እንዲሁም እድሜያቸው ከ14 ዓመት በላይ ከሆኑት ሴቶች ከአምስቱ አራቱ በህይወት ዘመናቸው ለማህፀን በር ካንሰር ተጋላጭ እንደሚሆኑም ተናግረዋል፡፡


የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ከ2011 ዓ.ም እስከ አሁን ባሉት ጊዜያት በዓመት 2 ጊዜ በ6 ወር ልዩነት ሁለት ዶዝ ክትባት ሲሰጥ መቆየቱን ሚኒስትሯ አስታውሰዋል፡፡


አለማቀፍ ጥናቶች መሰረት በማድረግ አንድ ጊዜ በተከተቡት እና ሁለት ጊዜ በተከተቡት ልጆች መካከል የክትባቱ ውጤታማነት ሲታይ ተመጣጣኝ የሚባል የመከላከል አቅም በማሳየቱ፣ ከዚህ ዓመት ጀምሮ አንድ ዶዝ ብቻ ይሰጣል ብለዋል፡፡



በ2016 ዓ.ም 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜያችው 14 ዓመት የሆናቸው ሴቶች ልጆች ለመከተብ ታቅዷል ተብሏል።


ክትባቱ በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ተቋማት፣ በግዝያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎችም እንደሚሰጥ ሰምተናል።


ወላጆች ወይም አሳዳጊዎች እድሜያቸው 14 ዓመት የሆናቸው ሴት ልጆች የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት እንዲወስዱ በማድረግ ግዴታቸውን እንዲወጡም በጤና ሚኒስቴር ጥሪ ቀርቧል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page