top of page

የካቲት 21፣2016 - የዓድዋ ድል አፍሪካዊያን ወታደራዊ ሳይንስ አዋቂ መሆናቸውን ለአለም ያሳየ ድል ነው ተባለ፡፡

ይህን ያሉት ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም አማካሪና ተኩስ አመራር ሀላፊ ናቸው፡፡


128ኛዉን የአድዋ የድል በዓል ምክንያት በማድረግ ''አድዋ የህብረ ብሔራዊነት ድምቀት የአንድነት ውጤት'' በሚል መሪ ሃሳብ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራስ መኮንን አዳራሽ ውይይት አካሂዷል።


ለዉይይት የሚሆን የመነሻ ጽሁፍ ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ፣ የጥንታዊ ኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ እና ፕሮፌሰር አየለ በክሪ አቅረርበዋል።


የአድዋ የድል በዓል አፍሪካዊያን ከነጮች እኩል የጦርነት ሳይንስ እንደሚያውቁ ያረጋገጠ እንደነበር ጀነራሉ አስረድተዋል።



የድል በዓሉን የምናከብርበት ዋነኛ ምክንያትም ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እንድትቀጥል ያደረገ ስለሆነ ነው ብለዋል ጄኔራል አለምሽት።


ለመላው ጥቁር ህዝብ ቀና ማለት ምክንያት የሆነው የአድዋ ድልን በሀገር ጉዳይም አንድ ለመሆን መጠቀም ደግሞ የአሁኑ ትውልድ ሃላፊነት ነው ብለዋል።


ያሬድ እንዳሻው



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


bottom of page