top of page

የካቲት 20 2017 - ኢሰመኮ በሰብአዊ ማብቶች ላይ ከሚሰሩ መንግስታዊ ካልሆኑ የመብት ተሟጋች ተቋማት ጋር እንደሚወያይ ተናግሯል

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ታህሳስ ወር ላይ ከተልኳቸው ውጪ ተንቀሳቅሰዋል በሚል በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የታገዱት የመብት ተሟጋች ተቋማት ጉዳይ በህግ አግባብ ብቻ ጉዳያቸው እንዲታይ ማሳሰቡን ተናግሯል፡፡


#የኢትዮጵያ_ሰብአዊ_መብቶች_ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው በቅርቡ የተሾሙት ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የታገዱት የመብት ተሟጋች ተቋማት ጉዳይ በህግ አግባብ ብቻ እንዲታይ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የስራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸውን ነግረውናል፡፡


የካቲት 17/2017 ዓ.ም ከባለስልጣን ማሰሪያ ቤት የስራ ሃላፊዎች ጋር መምከራቸውን የተናገሩት ኮሚሽነር ብርሃኑ በዚህም በሲቪል ማህበረሰብ ባለስልጣን የታገዱት የመብት ተሟጋች ተቋማት ጉዳያቸው ህግን ተከትሎ መፍትሔ እንዲገኝ ሃሳብ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡


በዚህም ከባለስልጣኑ የስራ ሃላፊዎች ጋርም መግባባት ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡


ኢሰመኮ በዛሬው እለትም በሰብአዊ ማብቶች ላይ ከሚሰሩ መንግስታዊ ካልሆኑ የመብት ተሟጋች ተቋማት ጋር እንደሚወያይ ተናግሯል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….



ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page