top of page

የካቲት 20፣2016 - የሰላም ሚኒስቴር በ45 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 9 ጀምሮ በሶስት ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጉን ተናገረ

  • Feb 28, 2024
  • 1 min read

ርዕሰ ጉዳዮቹ በሀገራዊ ጥቅም፣ ሀገራዊ እሴት እና የጋራ ማንነት ናቸው ተብሏል፡፡


የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ያህል በሀገራዊ ጥቅም ያምናል፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ብሔሮች የራሳቸው እሴት እንዳላቸው ሁሉ በሀገራዊ እሴት ያምናሉ ወይ፣ ካላቸው የተለያየ ማንነት ባለፈ አንድ በሚያደርግ የኢትዮጵያ ማንነት ላይ ያላቸው አመለካከት ምን ይመስላል? በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረዋል ሲሉ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የሰላም ሚኒስትር ድኤታው ከይረዲን ተዘራ አስረድተዋል፡፡


በውይይቱ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን እና ወጣቶች በ45ቱም የትምህርት ተቋማት ተሳትፈዋል ብለዋል፡፡


ተደርጓል በተባለው የውይይት መድረክ ከ20 ሺህ በላይ መምህራን እንደተሳተፉና የትምህርት ተቋማቱ ባላቸው የማህበረሰብ ሬዲዮ ለ40 ሚሊየን ሰዎች ተደራሽ ማድረግ ችለዋል ሲሉ ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል፡፡


በውይይቱና በምክክሩ ላይ የተገኙት ውጤቶች አርብ በአድዋ ሙዚየም ይፋ ይደረጋሉ ተብሏል፡፡


ያሬድ እንዳሻው




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።

ነሐሴ 7 2018 በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ። ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page