top of page

የካቲት 20፣2016 - በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች እርዳታ ጠባቂ ለሆኑ ለመጪው አንድ ዓመት እርዳታ ለማቅረብ 3.24 ቢሊዮን ያስፈልጋል ተባለ

በኢትዮጵያ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች እርዳታ ጠባቂ ለሆኑ ሰዎች ለመጪው አንድ ዓመት የሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ 3.24 ቢሊዮን ያስፈልጋል ተባለ።


እርዳታ ጠባቂ ለመሆን የተገደዱት ሰዎች ብዛት 21.4 ሚሊዮን ነው የተባለ ሲሆን የሚፈለገው ገንዘብ ከተገኘ 15.5 ሚሊዮን ሰዎች ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።


ሪፖርቱን ይፋ ያደረገው ዩኤን ኦቻ ከሚያስፈልገው 3.24 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 1.54 ቢሊዮን ዶላሩ ለቀለብ መስፈሪያ የሚሆን ነው ብሏል።


ድርቅ፣ ጎርፍ እንዲሁም ጦርነት በኢትዮጵያ ሚሊዮኖችን ለእርዳታ ጠባቂነት ዳርገዋቸዋል።



ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page