top of page

የካቲት 19 2017 - የደቡብ ሱዳኖቹ ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ጥቃት ቀንሷል ሲል የጋምቤላ ክልል ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Feb 26, 2025
  • 1 min read

ከዚህ ቀደም መነሻቸውን ከደቡብ ሱዳን ያደረጉ ታጣቂዎች ድንበር ተሻግረው በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ይታወሳል።


አሁን ግን በአመዛኙ ካለፉት ዓመታት አኳያ ጥቃቱ እየቀነሰ መጥቷል ሲል ክልሉ ተናግሯል።


#የጋምቤላ_ክልል የመንግስት ኮሚዮኒኬሽን ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡጁሉ ጌሌጅሎ ባለፉት ዓመታት በድንበር አዋሳኝ ባሉ ቀበሌዎች በርካታ ህጻናትና የቁም እንስሳት በታጣቂዎች እንደሚወሰዱ እና ጥቃት እንደሚደርስ አንስተው አሁን ላይ ግን ጥቃቱ ቀንሷል ብለዋል።


አቶ ኡጁሉ ጥቃቱ ቀንሷል ይበሉ እንጂ አሁንም ቢሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ታጣቂዎቹ እንቅስቃሴ እያደረጉ ስለመሆኑም ነግረውናል።

ግን ይሄ እንቅስቃሴ ያን ያህል ስጋት ላይ አይጥልም ብለዋል።


ከዚህ ቀደም በክልሉ በእነዚህ ታጣቂዎች ምክንያት በርካታ ጉዳት ደርሷል።


ክልሉን እና አካባቢውን የሚጠብቁ የፌዴራል ፖሊስና መከላከያ ሰራዊት አሉ ።


ሆኖም እነሱ ባሉበት ሁኔታ ህፃናትና እንስሳት በታጣቂዎቹ ሲጋዙ እና ጉዳት ሲደርስባቸው ነበር።


ምክንያቱስ ምንድን ነው? ብለን ለአቶ ኡጁሉ ላነሳንላቸው ጥያቄ ታጣቂዎቹ በትናንሽ ቡድኖች ተበታትነው በተለያዩ አቅጣጫዎች ስለሚንቀሳቀሱ ነው የሚል ምላሽም ሰጥተውናል።




ፍቅሩ አምባቸው

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page