top of page

የካቲት 19፣2016 - በጋምቤላ ክልል ለግጭት ምክንያት አንዱ የሆነዉ የሰብአዊ አቅርቦት ችግር ተፈቷል ሲል ክልሉ ተናገረ።

በክልሉ ለስደተኞች የሰብአዊ አቅርቦት ተቋርጦ ስለነበር ለግጭት ምክንያት ሆኖ ነበር ተብሏል።


ከፌዴራል መንግስት እና ከዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች በመነጋገር እና በመወያየት ተቋርጦ የቆየው የሰብዓዊ አቅርቦት ችግር በመፈታቱ አንደኛው የግጭት መነሻ፤ መፍትሄ እንዳገኘ ክልሉ አስረድቷል።


በክልሉ የተጠለሉ ስደተኞች የሰብዓዊ አቅርቦቱ ሲቋረጥም ሆነ ሲዘገይ ወደ አካባቢው የአርሶ አደር ማሣ በመግባት እና ሌሎት ጥፋቶችን ሲፈጸሙ ነበረ ሲሉ የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ኡጁሉ ጊሎ ነግረውናል።


የጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን ተፈናቅለው የመጡ ከ385 ሺህ በላይ ስደተኞች ያሉበት ክልል ሲሆን ይህም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ የሚኖርበት ክልል ያደርገዋል።


በተያያዘ ወሬ የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞችን እየተቀበለ እንዳለ አስረድተዋል።


ያሬድ እንዳሻው



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page