top of page

የካቲት 19፣2016 - በጋምቤላ ክልል ለግጭት ምክንያት አንዱ የሆነዉ የሰብአዊ አቅርቦት ችግር ተፈቷል ሲል ክልሉ ተናገረ።

  • sheger1021fm
  • Feb 27, 2024
  • 1 min read

በክልሉ ለስደተኞች የሰብአዊ አቅርቦት ተቋርጦ ስለነበር ለግጭት ምክንያት ሆኖ ነበር ተብሏል።


ከፌዴራል መንግስት እና ከዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች በመነጋገር እና በመወያየት ተቋርጦ የቆየው የሰብዓዊ አቅርቦት ችግር በመፈታቱ አንደኛው የግጭት መነሻ፤ መፍትሄ እንዳገኘ ክልሉ አስረድቷል።


በክልሉ የተጠለሉ ስደተኞች የሰብዓዊ አቅርቦቱ ሲቋረጥም ሆነ ሲዘገይ ወደ አካባቢው የአርሶ አደር ማሣ በመግባት እና ሌሎት ጥፋቶችን ሲፈጸሙ ነበረ ሲሉ የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ኡጁሉ ጊሎ ነግረውናል።


የጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን ተፈናቅለው የመጡ ከ385 ሺህ በላይ ስደተኞች ያሉበት ክልል ሲሆን ይህም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ የሚኖርበት ክልል ያደርገዋል።


በተያያዘ ወሬ የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞችን እየተቀበለ እንዳለ አስረድተዋል።


ያሬድ እንዳሻው



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page