top of page

የካቲት 16፣2016 - የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፅሐፍት አገልግሎት አዲስ ያስገነባውን ህንፃ አስመረቀ

  • sheger1021fm
  • Feb 24, 2024
  • 1 min read

አገልግሎቱ የተለያዩ የታሪክ መዛግብትን ላለፉት 80 ዓመታት ይዞ በማቆየት አንብቢያን እንዲያውቁት አድርጓል ተብሏል።


የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፅሐፍት አገልግሎት ወይም ወመዘክር በ80 ዓመት እድሜው የተላያዩ ታሪካዊ መፅሀፍትና ድርሳናትን ይዞ መቆየቱን የተነገረ ሲሆን ትውልዱ ለንባብ እንዲተጋ አድርጌያለሁ ብሏል።


የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ ‘’ወመዘክር ሀገሪቱ ያሏትን መንፈሳዊ፣ ቁሳዊ፣ ታሪካዊ እና ሀይማኖታዊ ትውፊቶችን ማሳያ የሆኑ ታሪክን ከትበው፣ ሁነትን መዝግበው የያዙ ሰነዶችና መፃህፍት’’ ይዟል ብለዋል።


‘’መንግስት አሁንም ለወመዝክር የሚያደርገውን ድጋፍ ይቀጥላል’’ ሲሉ ሰምተናቸዋል።


ወመዘክር ላይ የተለያዩ ምሁራን ጥናትና ምርምር ለማድረግ የተለያዩ መዛግብትን እንደሚጠቀሙ የተነገረ ሲሆን አሁንም ምሁራን በተቋሙ ጥናታቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page