top of page

የካቲት 14፣2016 - የገበያ ቅኝት - በሀገር ቤት ተመርቶ የሚቀርበው ጤፍ ለምን በዚህ ልክ ተወደደ?

  • sheger1021fm
  • Feb 22, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከተማ የሸቀጦች ዋጋ መናር የነዋሪውን ህይወት እንደፈተነው ተደጋግሞ ይነገራል።


ከቅርብ ጊዝ ወዲህ ጤፍን ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦች በአንድ ጀንበር ዋጋቸው ከፍ ማለቱ የሚታወቅ ነው፡፡


ነገር ግን ከሰሞኑ የሽንኩርት እና የቲማቲም ዋጋ እቀነሰ ቢሆንም የጤፍ ዋጋ ጨምሯል፡፡


ጤፍ ከወራት በፊትም ከስድስት ሺህ ብር ወደ አስራ ሁለት ሺህ፣ አስራ ሶስት ሺህ እና አስራ አራት ሺህ ብር በአንድ ጊዜ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።


ሸገር በአንዳንድ ወፍጮ ቤቶች ተዘዋውሮ ጤፍ ሲገበያይ የሰነበተበትን ዋጋ ተመልክቷል፡፡


በዚህም በየደረጃው ከ135 ብር እስከ 145 ብር በኪሎ እየተሸጠ መሆኑን አይቷል፡፡


እዚሁ በሀገር ቤት ተመርቶ የሚቀርበው ጤፍ ለምን በዚህ ልክ ተወደደ?


ለምንስ የአቅርቦት እና የፍላጎት አለመጣጣም ሊያጋጥም ቻለ?


ሸገር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮን ጠይቋል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page