top of page

የካቲት 14፣2016 - የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ሊያቀርብ የነበረው የጥናት ፅሁፍና የምርምር ውጤት ማቅረቢያ ፕሮግራም ተሰረዘ

  • sheger1021fm
  • Feb 22, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ በ10 ዓመት ጉዞ ውስጥ አብይ ኢኮኖሚው እንዴት አለፈ፣ ስኬቶቹና ፈተናዎቹስ ምንድናቸው በሚለው ዙሪያ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ሊያቀርብ የነበረው የጥናት ፅሁፍና የምርምር ውጤት ማቅረቢያ ፕሮግራም ተሰረዘ፡፡


ፕሮግራሙ በኢትዮጵ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ እና አስተዳደር ስኬቶች ፈተናዎችና በአጠቃላይ ኢኮኖሚው ላይ ምን ፈጠረ በሚለው ጉዳይ ላይም የጥናት ወረቀት ተለማቅረብ ታስቦ ነበር፡፡


የአስር ዓመት የልማት እቅድ እንዴት እንዳለፈ መመርመር፣ በኢትዮጵያ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት ተለዋዋጭነትና ፈተናን መተንተን በሚሉ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ለመስጠትም የተዘጋጀ ፕሮግራም መሆኑነን ሸገር ተረድቷል፡፡


ዛሬ ይህንኑ የጥናት ግኝትና ውጤት ለተጠሩ ለጋዜጠኞች ለመስጠት ሲሰናዱ የነበሩት ምሁራን በድንገት ጉባኤውን እንዲሰርዙ መገደዳቸውን ከቦታው በመገኘት ታዝበናል፡፡


በሰአቱ ለጋዜጠኞችና ለታዳሚያን ሊሰጥ የነበረው፤ ሀሳቡንና ጥናቱን ጠቅልሎ የያዘው የመግለጫ ወረቀት ተቆጥሮ ተሰብስቧል፡፡


የዛሬው መግለጫ የቀረበት ምክንያት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና እኔ በሌለሁበት አይካሄድም በሚል ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮቻችን ነግረውናል፡፡



ተሁቦ ንጉሴ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page