የካቲት 14፣2016 - የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ሊያቀርብ የነበረው የጥናት ፅሁፍና የምርምር ውጤት ማቅረቢያ ፕሮግራም ተሰረዘ
- sheger1021fm
- Feb 22, 2024
- 1 min read
በኢትዮጵያ በ10 ዓመት ጉዞ ውስጥ አብይ ኢኮኖሚው እንዴት አለፈ፣ ስኬቶቹና ፈተናዎቹስ ምንድናቸው በሚለው ዙሪያ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ሊያቀርብ የነበረው የጥናት ፅሁፍና የምርምር ውጤት ማቅረቢያ ፕሮግራም ተሰረዘ፡፡
ፕሮግራሙ በኢትዮጵ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ እና አስተዳደር ስኬቶች ፈተናዎችና በአጠቃላይ ኢኮኖሚው ላይ ምን ፈጠረ በሚለው ጉዳይ ላይም የጥናት ወረቀት ተለማቅረብ ታስቦ ነበር፡፡
የአስር ዓመት የልማት እቅድ እንዴት እንዳለፈ መመርመር፣ በኢትዮጵያ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት ተለዋዋጭነትና ፈተናን መተንተን በሚሉ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ለመስጠትም የተዘጋጀ ፕሮግራም መሆኑነን ሸገር ተረድቷል፡፡
ዛሬ ይህንኑ የጥናት ግኝትና ውጤት ለተጠሩ ለጋዜጠኞች ለመስጠት ሲሰናዱ የነበሩት ምሁራን በድንገት ጉባኤውን እንዲሰርዙ መገደዳቸውን ከቦታው በመገኘት ታዝበናል፡፡
በሰአቱ ለጋዜጠኞችና ለታዳሚያን ሊሰጥ የነበረው፤ ሀሳቡንና ጥናቱን ጠቅልሎ የያዘው የመግለጫ ወረቀት ተቆጥሮ ተሰብስቧል፡፡
የዛሬው መግለጫ የቀረበት ምክንያት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና እኔ በሌለሁበት አይካሄድም በሚል ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮቻችን ነግረውናል፡፡
ተሁቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il












Comments