top of page

የካቲት 13፣2016 - የራዳር መሳሪያ እጥረት ለስራው ፈተና እንደሆነበት የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ተናገረ

  • Feb 21, 2024
  • 1 min read

የተሽከርካሪዎችን የፍጥነት ወሰን ለመቆጣጠር የሚያግዘውን የራዳር መሳሪያ እጥረት ለስራው ፈተና እንደሆነበት የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ተናገረ፡፡


ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለሸገር እንደተናገረው የትራፊክ አደጋን ከሚፈጥሩ ምክንያቶች መካከል ቀዳሚው ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር እንደሆነ ይነገራል፡፡


ባለበት የሰው ሃይል እና የራዳር መሳሪያዎች እጥረት ምክንያት የፍጥነት ወሰን ቁጥጥር የሚሰራው አልፎ አልፎ መሆኑን የተናገሩት በባለስልጣኑ መስሪያ ቤቱ የዲጂታል ሚዲያ ባለሞያ የሆኑት አቶ መኳንንት ምናሴ ናቸው፡፡


ከሰሞኑ በሁለት ክፍለ ከተሞች ለ2 ሰዓታት ብቻ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ከ325 በላይ ሰዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ ሲያሽከረክሩ ተገኝተው እርምጃም ተወስዶባቸዋል ብለዋል፡፡


የፍጥነት ወሰን የቁጥጥር ባለሞያዎች በሌሉባቸው አካባቢዎች፤ አሽከርካሪዎች በአብዛኛው በፍጥነት እንደሚያሽከረክሩ የነገሩን አቶ መኳንንት ያለብንን የሰው ሃይል እጥረትን ለመቅረፍ በቅርቡ 400 ሰራተኞችን ለመቅጠር ተሰናድተናል እንዲሁም የመንገድ ካሜራዎችን በመግጠም ለመቆጣጠር አስበናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡


በሌላ በኩል የፍጥነት ወሰንን ለመገደብ በየመንገዱ የተሰራውና በአሽከርካሪዎች ዘንድ ቅሬታ የሚነሳበትን በኮንክሪት የሚሰራውን የፍጥነት መገደቢያ እያስቀረን በጎማ እየቀየርነው ነው፤ መገደቢያዎቹ ሲገነቡ አለም አቀፍ ደረጃዎችን አሟልተው ነው ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ5,000 በላይ ሰዎች በትራፊክ አደጋ ምክንያት ይሞታሉ ተብሏል፡፡


ከሟቾች መካከልም ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑት እግረኞች መሆናቸውንም ሰምተናል፡፡



ምንታምር ፀጋው




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።

ነሐሴ 7 2018 በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ። ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page