top of page

የካቲት 12፣2016 - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም መቋረጥ እንዳጋጠመው ተናገረ


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም መቋረጥ እንዳጋጠመው ተናገረ፡፡


ይህ የሆነውም በባንኩ መረጃ ማስተላለፊያ የፋይበር ኦፕቲክስ ገመድ ላይ በደረሰ ጉዳት መሆኑን ባንኩ አስረድቷል፡፡


በዚህም ምክንያት በባንኩ በቅርንጫፎች፣ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣ በሞባይል ባንኪንግ እንዲሁም ሲቢኢ ብር አገልግሎት ተቋርጧል ብሏል፡፡

አገልግሎቱን መልሶ ለማስጀመር ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት በከፍተኛ እርብርብ እየተሰራ ነው ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ደንበኞቹም በትዕግስት እንዲጠብቁ፣ ለተፈጠረው መጉላላትም ይቅርታ ጠይቋል፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page