top of page

የካቲት 11 2017 - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ ዘመን ለአንድ ዓመት ተራዘመ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ ዘመን ለአንድ ዓመት ተራዘመ።


የሕዝብ እነደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ስብሰባው የኮሚሽኑ የስራ ዘመን እንዲራዘም የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ አጽድቋል፡፡


ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያሳለፈው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሶስት ዓመታት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ከቀረበለት በኋላ ነው፡፡

ኮሚሽኑ የቀሩትን ስራዎች ማጠናቀቅ ይችል ዘንድም የስራ ዘመኑ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምፅ እና በሶስት ተቃውሞ አፅድቋል።


የምክር ቤቱ አባላት ኮሚሽኑ በተሰጠው ተጨማሪ የስራ ዘመን ቀሪ ስራዎችን እንዲያጠናቅቅ አሳስበዋል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page