top of page

የካቲት 1 2017 - ''የተረሳንና ባለቤት ያጣን ሆነናል'' የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች

  • sheger1021fm
  • Feb 8
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ኦሮሚያ ክልል ከጥቂት ዓመታት በፊት የአስተዳደር ወሰን ማካለላቸው ይታወሳል፡፡


በዚሁ ጊዜ ወደ ኦሮሚያ የተካለሉ የኮዬ ፈቼ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች ‘’የተረሳንና ባለቤት ያጣን ሆነናል’’ እያሉ ነው፡፡


የውሃ፣ የመብራት እና የመንገድ መሰረተ ልማት ሳይሟሉላቸው ወሰኑ መካለሉን ነዋሪዎ ነግረውናል፡፡


ታዲያ አሁን አካባቢውን የሚያስተዳድረውን አካል ሲጠይቁ ቤቱን የገነባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ነው መሰረት ልማቱን ማሟላት ያለበት እየተባል ያለመፍትሄ አመታት እያለፉ ነው ይላሉ፡፡


ችግሩ የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል ሆኖብናል ሲሉም ቅሬታቸውን ለሸገር ራዲዬ ነግረዋል፡፡





ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page