የአካቶ ትምህርት ዘርፉ ከሚጠይቀው ሰፊ ፋይናንስ አቅም እና ካለው የባለሙያ እጥረት አኳያ
- Feb 24
- 1 min read
የካቲት 17/2018
ትምህርት ለሁሉም ሰው እኩል ማዳረስ የትምህርት ሚኒስቴር ቀዳሚ ግቤ ነው በሚል በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የተለያዩ ስራዎች ሲሰራ ይታያል ፡፡
በተለይም አካል ጉዳት እና ሌሎች ጉዳቶች ላለባቸው ሰዎች ከሌላው እኩል የትምህርት ተጠቃሚ ማድረግ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ህግ ቀርፃ ሰው አሰልጥና ለመስራት ደፋ ቀና እያለች ነው፡፡
በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት ትምህርት ቤቶች የአካል ጉዳት ያለባቸው ህፃናት ከእድሜ እኩዮቻቸው እኩል ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ አለባቸው በሚል የአካቶ ትምህርት ትግበራ እንዲተገበር እያደረገ ነው፡፡
ነገር ግን ዘርፉ ከሚጠይቀው ሰፊ ፋይናንስ አቅም እና ካለው የባለሙያ እጥረት አኳያ አተገባበሩ ፈታኝ እያደረገው መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል፡፡
ሸገር ራዲዮ ያነጋገራቸው የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችም የሚያነሱት ይህንኑ ነው፡፡
በልዩ ፍላጎት የሰለጠነ በቂ የመምህራን ቁጥር አለመኖር፣ የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆን እና ሌሎች ችግሮች እንዳሉባቸው ተማሪዎቹ ያነሳሉ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴርም በበኩሉ ችግሮች እንዳሉ አምናለሁ የሚታዩ ክፍተቶችንም ለማጥበብ እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments