top of page

የአካል ጉዳተኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቿ ርግበ ገብረ-ሐዋሪያ የተባበሩት መንግስታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነት ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ።

  • Jun 10
  • 1 min read

ሰኔ 3/2018


የአካል ጉዳተኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቿ ርግበ ገብረ-ሐዋሪያ የተባበሩት መንግስታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነት ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ።


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በተጓደሉ አባላት ምትክ ባካሄደው ምርጫ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሚቴው አባል መሆን ችላለች።


የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች፣ህፃናት፣አካል ጉዳተኞችና አረጋዊያን መብቶች ኮሚሽነር የነበሩት ርግበ ገብረ-ሐዋሪያ ትናንት በኒውዮርክ በተካሄደው የሀገራት ሚስጥራዊ ምርጫ አሸናፊ ሆነዋል።


ከአባል ሀገራቱ የ133ቱን ድምፅ በማግኘት ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም ከተወዳደሩት አራተኛውን ከፍተኛ ድምፅ ማግኘታቸው ተነግሯል።

የተባበሩት መንግስታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነት ኮሚቴ፣በዓለም ዙሪያ የሀገራትን ከአካል ጉዳተኞች መብት ጋር የተገናኘ ደረጃ የሚፈትሽና የሚከታተል ነው ተብሏል።


በየጊዜው በመገናኘትም ይህንኑ የክትትልና ቁጥጥር ስራን እንደሚሰራ ተነግሯል።


የኮሚቴው አባል ሆነው የተመረጡት ርግበ ገብረ-ሐዋሪያ ይህ እድል ለኢትዮጵያ ሲሰጥ የመጀመሪያ መሆኑን ተናግረው ለአፍሪካም፣ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞችም ድምፃቸውን ለማሰማት ትልቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል።


ዘጠኝ አባላት ያለው ኮሚቴው የአራት ዓመት የስራ ዘመን እንደሚኖረውም ተነግሯል።


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page