top of page

የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በመንግስት አካላት እና በፖሊሲ አውጪዎች ላይ ጫና በማሳደር ስለ ትንባሆ አሳሳች መልክቶችን በማሰራጨት ንግዳቸውን ለማስፋፋት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።

  • Jan 13
  • 1 min read

ጥር 5/2018


የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በመንግስት አካላት እና በፖሊሲ አውጪዎች ላይ ጫና በማሳደር ስለ ትንባሆ አሳሳች መልክቶችን በማሰራጨት ንግዳቸውን ለማስፋፋት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።


ኢንዱስትሪዎቹ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ነን በሚል፣ የበጎ አድራጎት ስራን በማስታከክ እና በሌሎች ዘዴዎች የትምባሆ ስርጭትን ለማስፋፋት እየሰሩ ነው ተብሏል።


ከዚህ በተጨማሪም በዣንጥላዎች፣ በቲሸርቶች እና በመሰል ምርቶች ላይ ማስታወቂያዎችን እየሰሩ መሆኑም ተጠቅሷል።

የእነዚህን የኢንዱስትሪዎች ጫናን በመቋቋሙና ዘርፋን በመቆጣጠሩ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን የተሻለ ስራ ሰርቻለሁ ብሏል።


በዓለም ዓቀፍ ደረጃ 100 ሀገራት በተካተቱበት ጥናት፤ ኢትዮጵያ የትምባሆ ምርቶችን በመቆጣጠሩ የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግባለች ተብሏል።


በዚህ ጥናት ኢትዮጵያ የትምባሆ ምርቶችን በመቆጣጠር ከአፍሪካ 2 ከዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ሲል ተናግሯል።


ለዚህም ከአለም ጤና ድርጅት እውቅና ማግኘቱንም የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ዛሬ በሰጠው ማብራሪያ ተናግሯል።


ማንያዘዋል ጌታሁን

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page