ህዳር 11፣2016 - የተለያዩ መ/ቤቶች ሀላፊዎች ከገንዘብ ቅጣት እስከ ከሀፊላነት የማንሳት እርምጃ ተወስዶባቸዋል ተብሏል
- sheger1021fm
- Nov 21, 2023
- 1 min read
በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ያላግባብና ህግ ተጥሶ ወጭ የተደረገ ከ7 ቢሊየን ብር በላይ ለመንግስት እንዲመለስ በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ተጠይቆ 1.3 ቢሊየን ብር ተመላሽ መደረጉ ተሰማ፡፡
በሒሳብ አያያዝ ከፍተኛ ችግር አለባቸው የተባሉ ዩኒቨርሲቲዎችና የሌላም መ/ቤቶች ሀላፊዎች ላይ ደግሞ ከገንዘብ ቅጣት እስከ ከሀፊላነት የማንሳት እርምጃ ተወስዶባቸዋል ተብሏል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Комментарии